የምንሰጣቸው አገልግሎቶች

  1. የፋይናንሻልና ህጋዊነት ኦዲት

  2. የፐርፎርማንስ(የክዋኔ ኦዲት)

  3. የገቢ ኦዲት 

  4. የአከባቢ ኦዲት

  5. የልዩ ኦዲት(የማጭበርበር ኦዲት)

  6.  የስልጠና አገልግሎት

  7. የኦዲት ግኝትና ጥንቅር ግብረ-መልስ አገልግሎት

        የመስሪያ ቤቱ ስልጣንና ተግባር

  1. በከተማው አስተዳደር የመንግስት መ/ቤቶችና የመንግስት ልማት ድረጅቶች ላይ የፋይናንስና ህጋዊነት ኦዲት፣ የክዋኔ ኦዲት፣ የገቢ ኦዲት፣የአከባቢ ኦዲት፣ የመረጃ ቴክኖሎጂ ኦዲት ፣ ልዩ ኦዲትና እንደአስፈላጊነቱ ሌሎች ኦዲቶችን ያደርጋል ያስደርጋል።
  2. አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ከህዝብ አገልግሎት ሰጪና ከመንግስት ተቋማት ጋር ካለው ኮንትራት ውል አፈፃፀም ጋር የሚገናኙ ጉዳዮችን በተመለከተ የግል ድርጅቶችን አስፈላጊ መረጃዎችንና ሪፖርቶችን ሊመረምር ይችላል።
  3. በመንግስት መ/ቤቶች ወይም ድርጅቶች ኦዲት ግኝቶች ላይ ክትትል ያደርጋል፤ ስለአፈፃፀማቸውም ገምግሞ ግብረ-መልስ ይሰጣል። ስለሁኔታው ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ያደርጋል።
  4. ለመንግስት መ/ቤቶችና  ድርጅቶች የተሰጠ እርዳታ እና ብድር ኦዲት ያደርጋል፤ ያስደርጋል።
  5. ውጤታማ የሀብት አጠቃቀምን ለማሳደግና ወቅታዊ ለውሳኔ አጋዥ የሆነ የኦዲት ሪፖርት ለማቅረብ እንዲረዳው ሂሳብ ከመዘጋቱ በፊት የኦዲት ስራውን ሊጀምር ይችላል።
  6. ከፌደራልና ከክልል ዋና ኦዲተር መስሪያቤቶች ከግል ኦዲት ድርጅትና ከሚመለከታቸው መ/ቤቶች ጋር በመመካከር የኦዲት ስርዓትና ደረጃ በሚዳብርበት ሁኔታ የስራ ግንኙነትና ትብብር ያደርጋል።
  7. በከተማ አስተዳደር ውስጥ የኦዲት ሙያ ትክክለኛውን ፈር ይዞ እንዲዳብር ጥረት  ያደርጋል። አስፈላጊውን ቁጥጥር  ያደርጋል።
  8. አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የአስተዳደሩ መ/ቤት የውስጥ ኦዲተሮች የመ/ቤታቸውን ሂሳብና ንብረት ኦዲት አድርገው ውጤቶን እንዲገልፁለት ሊያደርግ ይችላል።
  9. የከተማ አስተዳደሩ የፋይናንስ ቢሮ ስለ ገንዘብ አጠባበቅ፣ የሂሳብ አያያዝና የንብረት አስተዳደር በተመለከተ በሚዘጋጀው መመሪያ ላይ አሰፈላጊውን ምክርና ሀሳብ ይሰጣል።
  10. ከሚመለከታቸው መ/ቤቶች እና ልማት ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለውስጥ ኦዲተሮች ስልጠና ይሰጣል፤ የውስጥ ኦዲት አሰራርን በማጥናት ለአስተዳደሩ አካላት ተገቢውን ምክር ይሰጣል፤ ያሰጣል።
  11. አንድ ሂሳብ የወንጀል ጥርጣሬ ባለበት ሁኔታና ታማኝነት በጎደለው አኳኋን መያዙን ለማመን በቂ ምክንያት ያለው እንደሆነ ሂሳቡን የሚመለከቱ ጽሑፎች፣ መዘክሮች፣ መዝገቦች፣ ሠነዶችና ሌሎች ተያያዥነት ያላቸው መረጃዎችን ያሽጋል፤
  12. በከተማ አስተዳደሩ የመንግሥት ሠራተኞች ህግ ውስጥ የተመለከቱት መሰረታዊ ዓላማዎችና የሰራተኛው መብትና ጥቅም እንደተጠበቀ ሆኖ የከተማው ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ መሰረት ለመሥሪያ ቤቱ አስፈላጊ የሆኑ ሠራተኞችን በራሱ ያስተዳድራል፣ ያሰናብታል፤ ይቀጥራል፣
  13. የሠራተኞቹን ደመወዝና ጥቅማ ጥቅሞች አጥንቶ ለምክር ቤት ያቀርባል ፣ ሲወሰን ተግባራዊ ያደርጋል፤
  14. መስሪያ ቤቱ በጀት አዘጋጅቶ ለምክር ቤት ያቀርባል፣ ሲፀድቅ፤ ስራ ላይ ያውላል።