የተቋማት ውስጥ ኦዲተሮች ተቋማት የሚበጀትላቸውን ሀብት ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡
ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ!
********************************
መንግስት ለህብረተሰቡ ይጠቅማሉ የበጃሉ ያላቸውን ዘላቂ የልማት ስራዋችና አገልግሎቶች በተግባር መሬት ላይ አውርዶ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ለማስቻል የመንግስት በጀትን ለሚጠይቁ ስራዎች ካለው ውስን ሀብት ቆንጥሮ ለነዚህ አገልግሎቶችና ዘላቂ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችና ለተለያዩ ዎጪዎች በጀት ይመድባል፡፡
ታዲያ ይህ ውስን የመንግስትና የህዝብ ሀብት ለታለመለት አላማ ለማዋልና ሁሉም ባለ በጀት መስሪያ ቤቶች በጀታውን በእቅድ ለያዟቸው ተግባራት በአግባቡ አውለው የመንግስትንና የህዝብን ሀብት ከብክነት፣ ምዝበራና ብልሹ አሰራር ለመከላከል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ይሰራሉ፡፡
ይሁን እንጅ በተለያዩ ምክንያቶች ከመንግስት ለተቋማት የሚበጀተው ውስን ሀብት በብልሹ አሰራር ምንያት ለብክነትና ምዝበራ ሲጋለጥ ይስተዋላል እንደ ግሎባል ፋይናንሻል ክራይም ዘገባ በ2023 በአለም ላይ 485 ቢሊየን ብር በላይ በሙስናና ብልሹ አሰራር ምክንያት ለምዝበራ እንደተጋለጠ ሲጠቅስ አሶሴሽን ኦፍ ሰርቲፋይድ ፍራውድ ኤግዛማይነር በምህፃረ ቃል ACFE በመባል የሚታወቀው ተቋም በበኩሉ ተቋማት በማጭበርበርና ሙስና አምስት በመቶ አመታዊ በጀታቸውን እንደሚያጡ ይጠቅሳል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት እነዚህንና መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ የማጭበርበር ኦዲት ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ሲሆን ስልጠናውን ለተሳታፊዎች የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ እንዳሉት ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ከመንግስት የሚፈቀድላቸውን ውስን በጀት ለተፈቀደላቸውና ለታለመለት አላማ በማዋል ተቋማት እራሳቸውን ከማጭበርበርና ምዝበራ የፀዱ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡
ዋና ኦዲተሩ አክለው በየተቋማቱ ጠንካራ የውስጥ ኦዲተሮች መኖራቸውን ጠቅሰው እነዚህ የተቋማት የውስጥ ኦዲተሮች ተቋማቱ የሚበጀትላቸውን ሀብት ከብክነት ለመታደግ ከፍተኛ ሚና ያላቸው መሆኑን ጠቅሰው እነዚህ የተቋማት የውስጥ ኦዲት ሰራኞች ሚናቸውን በልኩ መወጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡
********************************
የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም






















