News

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ባለድርሻ አካላትንና ተገልጋዮችን ያካተተ የመማክርት ጉባዔ ምስረታ አካሄደ።

**************************************በመማክርት ጉባኤ የምስረታ መድረክ የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ በመመስረት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የአዲት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል የከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በተገቢው ሁኔታ ለመምራትና አስተማማኝ መረጃ እንዲያገኝ የመንግስት ተቋማት የተመደበላቸውን ሀብት ሕግና መመሪያን ተከትለው በአግባቡ እንዲጠቀሙ በዕቅድና ኢኮኖሚያዊ በሆነ መንገድ በመምራት የሚጠበቅባቸው በመሆኑ በእቅድ የያዟቸውን ተግባራት ከግብ እንዲያሳኩና ህገወጥ የመንግስት ሀብትና ንብረት አጠቃቀምን በተመለከተ በኦዲት ተጣርቶ እንዲቀርብላቸው ከፍትህ አካላት የሚቀርቡ የኦዲት ይደረግልኝ ጥያቄዎችን በመቀበል ለውሳኔ የሚያግዝ የኦዲት ሥራ ውጤት በማቅረብ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሲያበረክት ቆይቷል ገልፀዋል፡፡

ሆኖም የአጋዥ አካላት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማትን እንዲሁም የተገልጋዮችን ተሳትፎ በማጎልበት በአገልግሎት አሰጣጡ ዙሪያ የሚታዩ ችግሮችን በመፍታት ግልጽነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል ይህ የመማክርት ጉባኤ መመስረቱን ገልፀው መማክርት ጉባኤው በከተማ አስተዳደሩ ያሉ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና ተገልጋይ ህብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ግልጽ የሆነ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት፤ በመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ተገልጋዩ ህብረተሰብ በአግባቡ እንዲረዳው ማስቻልን መሰረት ያደረገ አላማ ይኖረዋል ብለዋል።

የመማክርት ጉባኤው ከተገልጋይ ከሲቪክ ማህበራት ከባለድርሻ አካላትና የተቋሙ/ጽ/ቤት በሚወከሉ አካላት የሚመሰረት የመማክርት ጉባኤ ሲሆን ጉባኤው የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የመማክርት ጉባኤ ስራ አፈፃሚ ሰብሳቢና አባላትና በመምረጥ የመመስረቻ ጉባኤው ተጠናቋል ።

********************************

የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን አካሂዷል

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን ያካሄደ ሲሆን፤ በጉባኤው የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተዋል ።
የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት ስለተሰሩ ሥራዎች፣ የመንገድ ማስፋፊያዎች የኮሪደር ልማቱን ተሞክሮ በመውሰድ በፍጥነት እና በጥራት እንዲጠናቀቁ እየተደረገ ሳላለው ክትትል፣ የመብራት መቆራረጥን በዘላቂነት ለመፍታት ምን ታስቧል? ፣ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት በተለይ የጤና ተቋማት ግንባታ ላይ የተለየ ትኩረት ቢሰጥ የሚሉ ጥያቄዎች ከተነሱት መካከል ይጠቀሳሉ።
እንደ ሀገር እየተዋወቀ ያለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ በአዲስ አበባ በፍጥነት እና በትኩረት ተግባራዊ ቢደረግ የሚሉ እና ሌሎችም ጥያቄዎችም ከምክር ቤቱ አባላት ተነስተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከምክር ቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ መስጠታቸውን ከኢቢሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል


                   የኮሙንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
                  ሚያዚያ 22/2017

የኮሪደር ልማቱን በሁሉም የመዲናዋ አካባቢዎች ለማዳረስ በቅደም ተከተል እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ

መዲናዋ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት በሁሉም አካባቢዎች ለማዳረስ በቅደም ተከተል እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል፡፡
ከንቲባዋ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባው ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡
ለውጡን ተከትሎ ለህዝባችን ቃል ገብተን እና ራዕያችን አድርገን የተነሳነው አዲስ አበባን እንደስሟ ውብና ተወዳዳሪ ከተማ ለማድረግ ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፣ የህዝቡ ጥያቄ መሰረታዊ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ በተከናወነባቸው አካባቢዎች በርካታ ጥቅሞች እንደተገኙና በዚህም የመዲናዋ ነዋሪዎች ደስተኛ መሆናቸውንም ከንቲባ አዳነች አመልክተዋል፡፡
አዲስ አበባም እንደስሟ ውብ፣ለነዋሪዎቿ የምትመችና በዓለም አቀፍ ደረጃም ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን የኮሪደር ልማቱ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል፡፡
በርካታ ደረጃቸውን የጠበቁ መንገዶች፣ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ የአረንጓዴ ቦታዎች፣ የአውቶብስና የታክሲ መጫኛና ማውረጃ ፌርማታዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች እና ሌሎችንም ያካተተው የኮሪደር ልማት ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታን እያስገኘ እንደሚገኝም ከንቲባዋ አመላክተዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ ባልተዳረሰባቸው የመዲናችን አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎችንም የዚህ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ በቅደም ተከተል እየስራን ነው ብለዋል፡፡
በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ያረጁና በመፈራረስ ላይ የሚገኙ ቤቶችን አፍርሶ ለመገንባ ጊዜና ገንዘብ አስፈላጊ መሆኑን የተናገሩት ከንቲባ አዳነች፣ ህብረተሰቡ እንደተለመደው በትዕግስት እንዲጠብቅና ለስራውም ተሳታፊ እንዲሆን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳስበዋል ሲል የአዲስ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
የኮሙንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ሚያዚያ 22/2017

10ኛው የኦዲተሮች ልምድ ልውውጥ በድሬደዋ

10ኛው ሀገር አቀፍ የዋና ኦዲተሮች ውይይት በድሬደዋ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 10ኛው የክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶች የምክክር እና የልምድ ልውውጥ መድረክ በድሬደዋ ከተማ እየተካሄደ ነው።የድሬደዋ አስተዳደር ዋና ኦዲተር ፋኪያ መሐመድ በዚህ ወቅት÷የጋራ ምክክሩ ደረጃውን የጠበቀ የኦዲት ተግባራት በማከናወን የመንግስትና የህዝብ በጀት በአግባቡ ለታለመለት ተግባር እንዲውል የሚያስችሉ ግንዛቤዎችን ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል።
የልምድ ልውውጡ ደረጃውን የጠበቀ የክዋኔ ኦዲት ለመተግበር የሚያስችል ግንዛቤ የሚፈጥር መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡በተጨማሪም በየደረጃው በሚገኙ ተቋማት ውስጥ የተጠያቂነት ሥርዓትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል መደላድል እንደሚፈጥር ነው የገለፁት፡፡በውይይቱ ላይ የድሬደዋ አስተዳደር ምክርቤት አፈጉባዔ ፈትሂያ አደን፣ የየክልሎች እና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ዋና ኦዲተሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ለሶስት ቀናት በሚዘልቀው ውይይት ላይ ለተሞክሮ የሚያግዙ የተለያዩ ሰነዶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው የገኛል።

ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል

 “ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል” ቢሚል ርዕስ ከባለ ድርሻ አካላት (ኦዲት ተደራጊ ተቋማት) አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ።

መጋቢት 23/2017 ዓ.ም

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከባለድርሻ አካላት (ኦዲት ተደራጊ ተቋማት) አመራሮች ጋር “ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል”  በሚል ርዕስ ላይ በጁፒተር ሆቴል ውይይት አደረገ። ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ የውይይቱን ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን፤ በቀረበውም ሰነድ ላይ ተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየት ሰጥተዋል።

በመጨረሻም በቀረበው ጥያቄ ላይ  የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ የተከበሩ አቶ ማሾ ኦላና እና ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ  ምላሽ ሰጥተውበት ውይይቱ ተጠናቅቋል።

የ2016 ዓ.ም እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ አደረገ።

 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት የመ/ቤቱ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት በዛሬው ቀን ማለትም በ20/12/2016 ዓ.ም በኢትጵያ ስራ አመራር ኢንስቲትውት በዕቅድና በጀት ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ማሞ አማካኝነት ቀርቧል።

በመጨረሻም  በቀረበው ሰነድ ላይ የመ/ቤቱ ሰራተኞች አስተያየት እና ጥያቄ ያነሱ ሲሆን ለተነሱት ጥያቄዎች እና  አስተያየቶች የመ/ቤቱ ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ መልስ ሰጥተውበት ግምገማው ተጠናቅቋል።

የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ

ሀምሌ 09/2016 ዓ.ም የምትተክል ሀገር የሚያጸና ትውልድ በሚል መሪ ቃል የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መረህግብር በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 10 የችግኝ ተከላ መረሀ-ግብር ተካሄደ፤
በአረንጓዴ አሻራ መስክ የሚጠበቀው ውጤት እንዲመጣ ችግኝ መትከልና መንከባከብ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ ገለጹ
ያለምንም ልዩነት ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ – ግብር ስኬት በጋራ መቆም እንደሚገባ የልደታ ከ/ከተማ ክፍለ ከተማ ም/ ስራ አስፈፃሚ ክብርት ወይዘሮ ዮዲት ሰለሞን ገልጸዋል መ/ቤቱ በየዓመቱ የሚከናወነውን የችግኝ ተከላ ስራ የሚያከናውን ሲሆን ከመትከል ባሻገር ለችግኞች እንክብካቤ የሚደረግ መሆኑንና አምና ከተተከሉ ችግኞች መካከል 98 ፐርሰንቱ የጸደቀ ሲሆን የመ/ቤቱ ሰራተኞችና አመራሮችም በችግኝ ተከላው መረሀግብር ላይ መሳተፋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የዘጠኝ ወር አፈፃፀም ሪፖርት

መስሪያ ቤታችን የዘጠኝ(9) ወር አፈፃፀም ሪፖርት  ከአጠቃላይ የመ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር በእስቴይኢዚ(Stayeasy) ሆቴል  የገመገመ ሲሆን  የዘጥኝ ወር ሪፖርቱን ያቀረቡት የእቅድና በጀት ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ተወካይ  የሆኑት አቶ ደረጄ ማሞ ናቸው።  በቀረበው ሪፖርት ላይም ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ  ከሰራተኞች ጋር ውይይት አድርገዋል።

ዘጠነኛው የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከአጎራባች ክልሎች ጋር የሚያደርገው የኦዲት ስራዎች የአፈጻጸም ተሞክሮና ልምድ ልውውጥ መርሀ -ግብር ሶስተኛው ቀን ውሎ:-

በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር /ቤት አዘጋጅነት እየተካሄደ ያለው የልምድ ልውውጥ እና የጋራ የምክክር ጉባኤ ዛሬ ሶስተኛው ቀን ላይ ነው፡፡ በዛሬው ፕሮግራም አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር /ቤት እና ሲዳማ ክልል ዋና ኦዲተር /ቤት ተሞክሮአቸውን አቅርበዋል በከሰዓት ፕሮግራም በቀረቡት ሁለቱም ሰነዶች ላይ ውይይት ይደረጋል

ዘጠነኛው የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከአጎራባች ክልሎች ጋር የሚያደርገው የኦዲት ስራዎች የአፈጻጸም ተሞክሮና ልምድ ልውውጥ መርሀ -ግብር በሁለተኛው ቀን ውሎ:

በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መ/ቤት አዘጋጅነት እየተካሄደ ያለው የልምድ ልውውጥ እና የጋራ የምክክር ጉባኤ ዛሬ ሁለተኛውን ቀን ላይ ነው፡፡ በዛሬው ፕሮግራም የአማራ ዋና ኦዲተር መ/ቤት እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ተሞክሮአቸውን አቅርበዋል በከሰዓት ፕሮግራም በቀረቡት ሁለቱም ሰነዶች ላይ ውይይት ይደረጋል ።

ዘጠነኛው የአዲስ አበባ ከተማ  ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከአጎራባች ክልሎች ጋር የሚያደርገው የአዲት ስራዎች የአፈጻጸም ተሞክሮና ልምድ ልውውጥ መርሀ -ግብር መካሄድ ጀመረ

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከአጎራባች ክልሎች ጋር እያካሄደ ባለው የተሞክሮና የልምድ ልውውጥ መረሀ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ፤የአማራ ክልል ፤የሲዳማ ክልል ፤የደቡብ ምዕራብ ክልል፤የደቡብ ኢትይጵያ ክልል፤የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፤የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ፤የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር፤የሃራሪ ክልል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና እና ምክትል ኦዲተሮች የአፈጻጸም ተሞክሮና ልምዳቸውን በተዘጋጀው የቼክ ልስት መሰረት ለውይይት መነሻ ይሆን ዘንድ እያቀረቡ ይገኛሉ ።


የአዲስ አበባ ከተማ  ምክር ቤት ምክትል  አፈ ጉባኤ ወ/ት ፈይዛ መሐመድ ፤የመንግሥት በጀት ወጪ አስተዳደር ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጋትዌች ዎርን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻል ተገኝተው የኦዲት ስራዎች የአፈጻጸም ተሞክሮና ልምዶችን እያዳመጡ ነው።


መንግሥት ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሥራዎችን በሚፈለገው አግባብ ማስተዳደርና መምራት እንዲችል ህግና የአሰራር መመሪያን የተከተለ ጠንካራ የፋይናንስ የቁጥጥር ስርዓት መኖር አስፈላጊ መሆኑን በመረሀ-ግብሩ መክፈቻ ላይ የጠቆሙት የአዲስ አበበ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ት ፈይዛ  መሐመድ ኦዲት የመንግሥት ሀብትና ንብረትን ከብክነት ፣ከስርቆትና ሙስና ለመከላከል አይነተኛ መሣሪያ መሆኑን ተረድተን ሁሉችንም በተገኘንበት በዚሁ አግባብ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል ።


የዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤቶች የየዕለት የፋይናንስ ቁጥጥር ስራችሁን ከዓለም አቀፍ የኦዲት አተገባበር ተጨባጭ እንቅስቃሴዎች ጋር በማጣጣምና የዘርፉን ባለሙያዎች የሙያ ነጻነት በማክበር የመንግስት ሀብት ተጠብቆ እንዲጨምር ከማድረግ ረገድ ተወዳዳሪና ጠንካራ ሆናችሁ በመውጣት ኃላፊነታችሁን በአግባቡ ልትወጡ ይገባልም ሲሉ ምክትል አፈ -ጉባኤዋ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል ።


ከአጎራባች ክልሎች ጋር እየተደረገ ያለው የዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የተሞክሮና የልምድ ልውውጥ መድረክ የአፈጻጸም ሪፖርቶችን መነሻ ባደረገ መልኩ ክፍተቶችን ለይቶ መሙላትን ታሳቢ ባደረገ ውይይት እስከ መጪው አርብ ድረስ በልዩ ትኩረት የሚከናወን መሆኑን ከመረሀ-ግብሩ ለመረዳት ተችሏል ።4014:28