News

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና የተጠሪ ተቋማትን የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ገመገመ።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና የተጠሪ ተቋማትን የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ገመገመ።
ጥር 04/04/2018 አዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ፣ ለምክር ቤቱ ተጠሪ ከሆኑ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።
በመድረኩ ላይ ሁሉም ተጠሪ ተቋማት የስድስት ወር እቅድ አፈጻጸማቸውን ያቀረቡ ሲሆን በተለይም እንደ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ሪፎርም ያደረጉ ተቋማት ሪፎርሙ ያመጣው ለውጥና ተግዳሮቶችን ላይ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመልካም አስተዳደር ፤ሙስናን ከመከላከል አኳያ እና ከሌብነትና ከብልሹ አሠራር አንፃር በከተማዋ ለታየው የልማት ስራ ስኬት ተቋማቱ ስላበረከቱት ድርሻ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የውይይት መድረኩን የመሩት የምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ የተከበሩ ዶ/ር ማሾ ኦላና፤ ተጠሪ ተቋማቱ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ የታቀዱ ስራዎችን ብቻ ሳይሆን፣ ከዚያም በላይ የሆኑ ተግባራትን በፍጥነትና በጥራት ማከናወናቸው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም ተቋማቱ እርስ በእርስና ከሌሎች አካላት ጋር በቅንጅት በመስራታቸው ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡን ተናግረዋል፤ በተጨማሪም የላቀ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማረጋገጥ ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ጭምር ገልፀዋል።
የመንግስት ዋና ተጠረው፤ በተጨማሪም የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ማጠናከር፣ የህጎችን ተፈጻሚነት በኦዲት መፈተሽ እና የህዝብና የመንግስት ሀብት በግልጽነትና በተጠያቂነት መመራቱን ማረጋገጥ እንደሚገባ አቅጣጫ አሰቀምጠዋል።
የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ማሾ ኦላና አክለውም፣ በባለፈው በጀት ዓመት የታዩ መልካም አፈጻጸሞችን በማስቀጠልና ውስንነቶችን በመለየት ተቋማዊ ጥንካሬን መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ የተሳተፉ የተጠሪ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች በበኩላቸው፣ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ቀሪ የትኩረት ስራዎችን እንደሚያከናውኑ ገልጸዋል። የከተማውን ነዋሪ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በህግ የተሰጣቸውን ስልጣንና ኃላፊነት በመጠቀም በትጋት ለመስራት ቃል ገብተዋል.። የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ክዋኔ ኦዲት ዋና አላማ ለመልካም አስተዳደር፣ ለተጠያቂነት እና ለግልፀኝነት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግን ያለመ ነው።

ክዋኔ ኦዲት ዋና አላማ ለመልካም አስተዳደር፣ ለተጠያቂነት እና ለግልፀኝነት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግን ያለመ ነው።
***********************************************
በአሁኑ ወቅት የተቋማትን ስራ ውጤታማነት ለማረጋገጥና አላስፈላጊ ብክነትን ለመቀነስ የክዋኔ ኦዲት (Performance Audit) ወሳኝ መሆኑ የታመነ ነው። የክዋኔ ኦዲት ተቋማት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በምን ያህል ደረጃ እየተወጡ እንደሆነ የሚመዘንበት አይነተኛ መሳሪያ በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩን ተቋማት አፈፃፀም የተሻለ ለማድርግ በሶስት ዙር ለተመረጡ ከከተማ አስተዳደሩ ለተውጣጡ የውስጥ ኦዲተሮች የክዋኔ ኦዲት ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡

ለሁለተኛ ዙር የክዋኔ ኦዲት ስልጠና የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲት መስሪያ ቤት የክዋኔ ኦዲት ማናጀር የሆኑት አቶ መስፍን ውቤ እንዳሉት የአፈጻጸም/ክዋኔ ኦዲት አንድ ተቋም ግቡን ለማሳካት ሀብቱን እንዴት በብቃት እንደሚጠቀም የሚመረምር ገለልተኛ፣ ተጨባጭ እና አስተማማኝ ግምገማ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ ቅልጥፍናና ውጤታማነትን በመገምገም፣ መሻሻል ያለባቸውን ቦታዎች በመለየት ለተቋማት የላቀ አፈፃፀም ምክረ ሃሳብ በማቅረብ በትኩረት የሚሰራ ነው ብለዋል።

አቶ መስፍን አክለው የክዋኔ ኦዲት በዋናነት በሶስት የ”E” መርሆዎች፤ Economy/ቁጠባ Efficiency/ብቃት Effectiveness/ውጤታማነትን አጣምሮ የያዘ መሆኑን ጠቅሰው የክዋኔ ኦዲት በመንግስት ሴክተር ተቋማት ውስጥ ለተሻሻለ ኢኮኖሚ፣ ቅልጥፍና እና ውጤታማነት አስተዋፅኦ በማድረግ፤ ለመልካም አስተዳደር፣ ለተጠያቂነት እና ለግልጽኝነት አሰራር የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግን ዓላማ ያደረገ የኦዲት ዘርፍ ነው ብለዋል፡፡
*****************************************
መጋቢት 3/2018 ዓ.ም

ኦዲተሮች የሚባክነውን ውስን የመንግስት እና የህዝብ ሀብት ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ፡፡

ኦዲተሮች የሚባክነውን ውስን የመንግስት እና የህዝብ ሀብት ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ፡፡

በተለያዩ ተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉ የማጭበርበር Fraud ድርጊቶችን ተከትሎ የልዩ ኦዲት አስፈላጊነት እና ሚና በከፍተኛ ሁኔታ ትኩረት እየሳበ ይገኛል መንግስታዊና የግል ተቋማት ሙስስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከልና ተጠያቂነትን ለማስፈን ተቋማት መፍትሄ የሚሏቸውን አማራጮች ሲወስዱ ይስተዋላል ይሁን እንጂ በሚፈለገው ልክ ውጤት አምጥቷል ለማለት አያስደፍርም።

በመሆኑም የማጭበርበር ተግባራት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት ለማስቀረት በእውቀትና በክህሎት የሚመራ ኦዲተር ማፍራት ወሳኝ ሚና ያለው በመሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከከተማ አስተዳደሩ ለተውጣጡ የተመረጡ የውስጥ ኦዲተሮች ስለ ማጭበርበር/ ፍራውድ ተግባራት በሶስት ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

የአዲ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ ለሰልጣኞች ባስተላለፉት መልዕ እንዳሉት ተቋማት በአሰራራቸው ቀልጣፋና ፍትሀዊ አገልግሎት ከመስጠት ይልቅ በሙስናና ብልሹ አሰራር ምክንያት ተገልጋዩንና ህብረተሰቡን በአግባቡ ማገልገል ካልቻሉ ህብረተሰቡ በተቋሙ ብሎም በመንግስት አመኔታ ሊያጣ ይችላል ይህ እንዳይሆን ግን የሚሰሩ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ቀድሞ የመቆጣጠርና ተፈፅሞ ሲገኝም ተገቢ ማስተከካከያ እንዲሰጥ ለማድረግ የኦዲተሩ ሚና የላቀ ነው ብለዋል።

ዋና ኦዲተሩ አክለው ሙስናና ብልሹ አሰራር የሀገር ኢኮኖሚን በእጅጉ የሚጎዳ መሆኑን ጠቅሰው በተቋማት ውስጥ ያሉ ሁሉም የውስጥ ኦዲተሮች በያገባኛል ስሜት የሚባክነውን ውስን የመንግስት እና የህዝብ ሀብትን ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ለሠራተኞች የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ

በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ለሠራተኞች የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ
***********************************
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ እንደገለፁት መልካም ስነ ምግባርና ሙስናን መዋጋት ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ሳይሆን የእያንዳንዱ ሰራተኛ ድርሻና ተሳትፎ መሆኑን በመጥቀስ ሰራተኛው ስራውን በቅንነትና በታማኝነት በመስራት ለሌሎች አርአያ መሆን ይገባል ብለዋል፡፡

አክለውም የዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የከተማዋን ሀብትና ንብረት በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚያረጋግጥ ተቋም እንደመሆኑ መጠን የማጭበርበር ወይም የልዩ ኦዲትን በዳይሬክቶሬት ደረጃ በአዲስ መልክ በማደራጀት ሙስናንና ማጭበርበርን በመፋለም በግምባር ቀደምትነት የሚጠቀስ እንደመሆኑ ፣ የሠራተኞቹ የሥነ-ምግባር ደረጃ ከማንኛውም ተቋም በላይ አርአያነት ያለው ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።

የመንግስት ልማት ድርጅት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳሬክቶሬት አቶ ንጉስ ሽመልስ በበኩላቸው ሙስናን መከላከል የሚቻለው በጠንካራ የሕግ ተፈጻሚነት ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱ ሠራተኛ የሥነ-ምግባር ባለቤት ሲሆንና የሙስናን አፀያፊነት በልኩ ሲረዳ መሆኑን ጠቅሰው ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በሥራ ላይ የሚያጋጥሙ የሥነ-ምግባር ብዥታዎችን ለመቅረፍና ሙያዊ ግዴታን በብቃት ለመወጣት የተሻለ ግንዛቤ መፍጠርን ያለመ ነው ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በቀጣይም የሙስና መከላከል ስትራቴጂውን በማጠናከር፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሠራር ለመገንባት እንደሚሠራ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ ገልፀዋል።
*********************************
ሚያዝያ 9/2018 ዓ.ም
የኮሙንኬሽን ዳይሬክቶሬት

4ኛው የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተሮች አመታዊ የምክክር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል፤

4ኛው የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተሮች አመታዊ የምክክር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል፤
በጉባኤው የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉን ጨምሮ ሌሎች የክልል እና የከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተሮች ተሳትፈውበታል፡፡
በጉባኤው ላይ የተገኙት የዘርፉ አመራሮች በዋናነት በፌዴራል በክልሎች እና በከተማ አስተዳደሮች መካከል ያለውን የኦዲት አሰራር ለማዘመን እና የተሻሉ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ የሚያስችል መድረክ መሆኑ ታምኖበታል፡

አለማቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ተከበረ!

“ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት”

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን የመስሪያ ቤቱ አመራርና ሰራተኞች በተለያዩ ሁነቶች አከበሩ፡፡

********************************

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አምንቴ መቻሉ በመርሀ-ግብ ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሚያዝያ 21 ቀን 1998 ዓ.ም ባካሔደው ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባው ላይ የኤፌዴሪ ህገ መንግስት የፀደቀበትን ህዳር 29 ቀን የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ተብሎ በአገር አቀፍ ደረጃ እንዲከበር ሲወስን የውሳኔው ዓላማ የኢትዮጵያ ህዝቦች መክረውና ፈቅደው ያጸደቁት ህገ-መንግስት ያስገኘላቸውን ጥቅሞች እንዲያስቧቸው መብቶችና ነጻነቶቻቸውን ጠብቀው ማቆየት ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ የሚተዋወቁበት ባህላቸውን፣ ቋንቋቸውንና ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት፤አገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚወያዩበት፤ የጋራ እምነቶቻቸውንና ተስፋቸውን የሚጋሩበትን ሁኔታ ለመፍጠር ነው ብለዋል፡፡

ዋና ኦዲተር አምንቴ መቻሉ አክለው የብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በ1999 ዓ.ም በፌዴሬሽን ምክር ቤት አዘጋጅነት ”ሕገ-መንግስታዊ ቃል ኪዳን የአብሮነታችን መገለጫ ነው” በሚል መሪቃል በአዲስ አበባ ከተማ የተከበረ ሲሆን ይህም ላለፉት 19 ዓመታት በተከታታይ በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር መቆየቱን ገልፀው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለሕብረ ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል ሂዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሚከበር መሆኑን ጠቅሰው የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤትም ከዚህ በመነሳት ይህን ህገ-መንግስታዊ ዋስትና የተረጋገጠበት የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ ይገኛል ብለዋል፡፡

ለተሳታፊዎች የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት የኮልፌ ክ/ከተማ የብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ት/ቤት የማስፈፀም የአቅም ግንባታ ስራዎች አስተባሪ አቶ ፍቃዱ ቀቀባ አስተባባሪ እንዳሉት የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብት መከበር ሕገ መንግሥታዊ ዋስትና ያረጋገጠው የኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት የጸደቀበትን ቀን ህዳር 29 በየዓመቱ በተለያዩ ሁነቶች ላለፉት 19 ዓመታት ሲከበር መቆየቱን አስታውሰው በዚህ አመት “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል ለ20ኛ ግዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሲከበር በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ፌዴራላዊ ሥርዐት ማእቀፍ የተገነባ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ሥር እንዲሰድና እንዲዳብር ማደረግን አላማ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡

********************************

ህዳር 19/2018 ዓ.ም

የኮምንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

አለማቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ተከበረ!

አለማቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ተከበረ!

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት «ትውልድን በሥነ-ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!» በሚል መሪ ቃል በዓለም ለ22ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ21 ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ ባስተላለፉት መልክት ተቋማችን ከሁሉም በላይ በሙስና ጉዳይ ተልእኮ ወስደን በተደራጀና ተቋማዊ አሰራር በሆነ ሁኔታ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን መከላከል እንደ ሀገር ደግሞ አዋጆች ደንቦች ወጥተዋል ይህን መሰረት አድርገን እንደ አንድ የኦዲት ባለሙያ ሙስናን መከላከል ብቻ ሳይሆን በሙስናና ብልሹ አሰራር የባከነን የመንግስትና የህዝብ ሀብት ማስመለስ ይገባል ብለዋል።

ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ አክለው በመስሪያ ቤቱ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለመታገል አደረጃጀትና አንድ የስራ ክፍል ፈጥሮ በተግባር በፀረ ሙስናና ብልሹ ከሰራር ትግል ውስጥ መሆኑን በመግለፅ ሁሉም ሰራተኞች ለዛሬ ሳይሆን ለነገው ትውልድ ከሙስናንና ብልሹ አሰራር የፃዳች ሀገር ለማስረከብ ሚናውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ የሕግ ረቂቅ ምርምር እና ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል ሳላህ ሙስና ማለት በግል ወይም በቡድን፣ በፖለቲካ መሪዎች ወይም በቢሮክራቶች ስልጣንና ሀላፊነትን መከታ በማድረግ የህዝብን ጥቅምና ፍላጎት ለግል ጥቅም የማዋል ኢ-ስነምግባርዊ ድርጊት ሲሆን ሀገራችን ኢትዮጵያ ይህንና መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ አለም አቀፍና አህጉራዊ የፀረ-ሙስና ኮንቬንሽኖችን የተቀበለችና በርካታ እርምጃዎች እየወሰደች ትገኛለች እንደምትገኝ ጠቅሰው የስልጠናው ተሳታፊዎች የሙስና ወንጀልን ከመፈጸም በመቆጠብ ሌሎች እንዳይፈጽሙ ለማድረግ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

ህዳር 18/2018 ዓ.ም

የኮምንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

አለማቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ተከበረ!

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የዲጂታል ቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርዓት ለማስጀመር የሙከራ ስልጠና ሰጠ፡፡

የሙከራ ማስጀመሪያ ስልጠና የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጌትነት ባንቴ እንዳሉት የዲጂታል ቅሬታ ማቅረቢያ ኢ ሰርቪስ የተቋማት የውስጥና የውጭ ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ እና ሁኔታ በየትኛውም ጊዜ ቅሬታቸውን ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው የበለፀገው ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለተቋማት አገልግሎታቸውን ለማዘመንና የተገልጋዮቻቸውን የአገልግሎት እርካታ ለማሰደግ ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ በበኩላቸው የሚሰጡ አገልግሎቶች የህብረተሰቡንና የባለድርሻ ተቋማትን የአገልግሎት እርካታ ለመፍጠርና ለማሳደግ የሚሰራ መሆኑን ገልፀው በአገልግሎት ሂደት የሚፈጠሩ ቅሬታዎችን ለማቅረብና ለመፍታት ከወረቀት ንክኪ ነፃ የዲጂታል ቅሬታ ማቅረቢያ ስርዓት መፈጠሩ ተገልጋዩ ባለበት ሁኔታና ቦታ ለሚያቀርበው ቅሬታ እልባት ለመስጠት ትልቅ እድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡

ዋና ኦዲተሩ አክው የውስጥ ቅሬታዎች በአቻ ፎረምና በስትራቴጂክ ካውንስል ቅሬታዎች ቀርበው የሚፈቱ መሆኑን ገልፀው እነዚህ አማራጮችን ለማያገኙ ተገልጋዮች ይህ የዲጂታል ቅሬታ ማቅረቢያ ስርዓት ተገልጋዩንና ተቋማትን የበለጠ የሚያቀራርብና ለችግሮች እልባት ለመስጠት ተጠቃሽ ሚና አለው ብለዋል፡፡

******************************

የኮምንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ህዳር 12/2017 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በልዩ ኦዲት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አጠናቀቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በልዩ ኦዲት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አጠናቀቀ፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለአምስት ተከታታይ ቀናት በልዩ ኦዲት ላይ ያጠነጠነ ስልጠና ለልዩ ኦዲት ባለሙያዎቹ ስልጠና ሰጥቷል፡፡

ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ እንዳሉ በልዩ ኦዲት ስራዎቻችን የተቀመጡትን አለማቀፍ ስታንደርዶች በመጠበቅ ባለበጀት መ/ቤቶች የተበጀተላቸውን የህዝብ ሃብት በአግባቡ መጠቀማቸውን ለማረጋገጥና በማወቅም ሆነ በለማወቅ ለሚሰሯቸው ስህተቶች መፍትሄ እዲያበጁ ማስቻል እንዲሁም የሀገርና የህዝብን ሀብት ከብክነት ለመጠበቅና አንደ አንድ የመንግስት ኦዲት አድራጊ ተቋም ሁሉም የኦዲት ባለሙያ ሚናውን እንዲወጣ ለማስቻል ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡

ዋና ኦዲተ አመንቴ መቻሉ አክለው የኦዲት ግኝትና ሂሳብ ጉለት ሲገኝ ገንዘብ ተመላሽ ማድረግ ብቻ ሳይሆን የተጠያቂነት አሰራር ስርዓትን ለማስፈን አስፈላጊውን የህግ ሂደት በመከተል ግልፀኝነትና የተጠያቂነት አሰራር ስረዓት እንዲሰፍን መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በስልጠናው ማብቂያ በሰጡት አስተያየት ስልጠናው በቀጣይ ስራቸው ላይ የተሻለ አቅም የሚሰጡ ጠቃሚ እውቀትና ክህሎቶችን ያስጨበጣቸው መሆኑን ጠቅሰው በተለይ በልዩ ኦዲት ስራ ላይ ሊሚያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችና ስጋቶችን በግልፅ ያመላከተ በመሆኑ የልዩ ኦዲት ስራዎቻችንን ውጤታማ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል፡፡


የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም

የተቋማት ውስጥ ኦዲተሮች ተቋማት የሚበጀትላቸውን ሀብት ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡

የተቋማት ውስጥ ኦዲተሮች ተቋማት የሚበጀትላቸውን ሀብት ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡

ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ!

********************************

መንግስት ለህብረተሰቡ ይጠቅማሉ የበጃሉ ያላቸውን ዘላቂ የልማት ስራዋችና አገልግሎቶች በተግባር መሬት ላይ አውርዶ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ለማስቻል የመንግስት በጀትን ለሚጠይቁ ስራዎች ካለው ውስን ሀብት ቆንጥሮ ለነዚህ አገልግሎቶችና ዘላቂ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችና ለተለያዩ ዎጪዎች በጀት ይመድባል፡፡

ታዲያ ይህ ውስን የመንግስትና የህዝብ ሀብት ለታለመለት አላማ ለማዋልና ሁሉም ባለ በጀት መስሪያ ቤቶች በጀታውን በእቅድ ለያዟቸው ተግባራት በአግባቡ አውለው የመንግስትንና የህዝብን ሀብት ከብክነት፣ ምዝበራና ብልሹ አሰራር ለመከላከል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ይሰራሉ፡፡

ይሁን እንጅ በተለያዩ ምክንያቶች ከመንግስት ለተቋማት የሚበጀተው ውስን ሀብት በብልሹ አሰራር ምንያት ለብክነትና ምዝበራ ሲጋለጥ ይስተዋላል እንደ ግሎባል ፋይናንሻል ክራይም ዘገባ በ2023 በአለም ላይ 485 ቢሊየን ብር በላይ በሙስናና ብልሹ አሰራር ምክንያት ለምዝበራ እንደተጋለጠ ሲጠቅስ አሶሴሽን ኦፍ ሰርቲፋይድ ፍራውድ ኤግዛማይነር በምህፃረ ቃል ACFE በመባል የሚታወቀው ተቋም በበኩሉ ተቋማት በማጭበርበርና ሙስና አምስት በመቶ አመታዊ በጀታቸውን እንደሚያጡ ይጠቅሳል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት እነዚህንና መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ የማጭበርበር ኦዲት ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ሲሆን ስልጠናውን ለተሳታፊዎች የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ እንዳሉት ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ከመንግስት የሚፈቀድላቸውን ውስን በጀት ለተፈቀደላቸውና ለታለመለት አላማ በማዋል ተቋማት እራሳቸውን ከማጭበርበርና ምዝበራ የፀዱ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡

ዋና ኦዲተሩ አክለው በየተቋማቱ ጠንካራ የውስጥ ኦዲተሮች መኖራቸውን ጠቅሰው እነዚህ የተቋማት የውስጥ ኦዲተሮች ተቋማቱ የሚበጀትላቸውን ሀብት ከብክነት ለመታደግ ከፍተኛ ሚና ያላቸው መሆኑን ጠቅሰው እነዚህ የተቋማት የውስጥ ኦዲት ሰራኞች ሚናቸውን በልኩ መወጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡

********************************

የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ባለድርሻ አካላትንና ተገልጋዮችን ያካተተ የመማክርት ጉባዔ ምስረታ አካሄደ።

**************************************በመማክርት ጉባኤ የምስረታ መድረክ የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ በመመስረት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የአዲት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል የከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በተገቢው ሁኔታ ለመምራትና አስተማማኝ መረጃ እንዲያገኝ የመንግስት ተቋማት የተመደበላቸውን ሀብት ሕግና መመሪያን ተከትለው በአግባቡ እንዲጠቀሙ በዕቅድና ኢኮኖሚያዊ በሆነ መንገድ በመምራት የሚጠበቅባቸው በመሆኑ በእቅድ የያዟቸውን ተግባራት ከግብ እንዲያሳኩና ህገወጥ የመንግስት ሀብትና ንብረት አጠቃቀምን በተመለከተ በኦዲት ተጣርቶ እንዲቀርብላቸው ከፍትህ አካላት የሚቀርቡ የኦዲት ይደረግልኝ ጥያቄዎችን በመቀበል ለውሳኔ የሚያግዝ የኦዲት ሥራ ውጤት በማቅረብ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሲያበረክት ቆይቷል ገልፀዋል፡፡

ሆኖም የአጋዥ አካላት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማትን እንዲሁም የተገልጋዮችን ተሳትፎ በማጎልበት በአገልግሎት አሰጣጡ ዙሪያ የሚታዩ ችግሮችን በመፍታት ግልጽነት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል ይህ የመማክርት ጉባኤ መመስረቱን ገልፀው መማክርት ጉባኤው በከተማ አስተዳደሩ ያሉ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና ተገልጋይ ህብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ግልጽ የሆነ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት፤ በመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ተገልጋዩ ህብረተሰብ በአግባቡ እንዲረዳው ማስቻልን መሰረት ያደረገ አላማ ይኖረዋል ብለዋል።

የመማክርት ጉባኤው ከተገልጋይ ከሲቪክ ማህበራት ከባለድርሻ አካላትና የተቋሙ/ጽ/ቤት በሚወከሉ አካላት የሚመሰረት የመማክርት ጉባኤ ሲሆን ጉባኤው የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የመማክርት ጉባኤ ስራ አፈፃሚ ሰብሳቢና አባላትና በመምረጥ የመመስረቻ ጉባኤው ተጠናቋል ።

********************************

የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን አካሂዷል

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን ያካሄደ ሲሆን፤ በጉባኤው የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተዋል ።
የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት ስለተሰሩ ሥራዎች፣ የመንገድ ማስፋፊያዎች የኮሪደር ልማቱን ተሞክሮ በመውሰድ በፍጥነት እና በጥራት እንዲጠናቀቁ እየተደረገ ሳላለው ክትትል፣ የመብራት መቆራረጥን በዘላቂነት ለመፍታት ምን ታስቧል? ፣ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት በተለይ የጤና ተቋማት ግንባታ ላይ የተለየ ትኩረት ቢሰጥ የሚሉ ጥያቄዎች ከተነሱት መካከል ይጠቀሳሉ።
እንደ ሀገር እየተዋወቀ ያለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ በአዲስ አበባ በፍጥነት እና በትኩረት ተግባራዊ ቢደረግ የሚሉ እና ሌሎችም ጥያቄዎችም ከምክር ቤቱ አባላት ተነስተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከምክር ቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ መስጠታቸውን ከኢቢሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል


                   የኮሙንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
                  ሚያዚያ 22/2017

የኮሪደር ልማቱን በሁሉም የመዲናዋ አካባቢዎች ለማዳረስ በቅደም ተከተል እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ

መዲናዋ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት በሁሉም አካባቢዎች ለማዳረስ በቅደም ተከተል እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል፡፡
ከንቲባዋ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባው ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡
ለውጡን ተከትሎ ለህዝባችን ቃል ገብተን እና ራዕያችን አድርገን የተነሳነው አዲስ አበባን እንደስሟ ውብና ተወዳዳሪ ከተማ ለማድረግ ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፣ የህዝቡ ጥያቄ መሰረታዊ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ በተከናወነባቸው አካባቢዎች በርካታ ጥቅሞች እንደተገኙና በዚህም የመዲናዋ ነዋሪዎች ደስተኛ መሆናቸውንም ከንቲባ አዳነች አመልክተዋል፡፡
አዲስ አበባም እንደስሟ ውብ፣ለነዋሪዎቿ የምትመችና በዓለም አቀፍ ደረጃም ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን የኮሪደር ልማቱ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል፡፡
በርካታ ደረጃቸውን የጠበቁ መንገዶች፣ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ የአረንጓዴ ቦታዎች፣ የአውቶብስና የታክሲ መጫኛና ማውረጃ ፌርማታዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች እና ሌሎችንም ያካተተው የኮሪደር ልማት ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታን እያስገኘ እንደሚገኝም ከንቲባዋ አመላክተዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ ባልተዳረሰባቸው የመዲናችን አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎችንም የዚህ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ በቅደም ተከተል እየስራን ነው ብለዋል፡፡
በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ያረጁና በመፈራረስ ላይ የሚገኙ ቤቶችን አፍርሶ ለመገንባ ጊዜና ገንዘብ አስፈላጊ መሆኑን የተናገሩት ከንቲባ አዳነች፣ ህብረተሰቡ እንደተለመደው በትዕግስት እንዲጠብቅና ለስራውም ተሳታፊ እንዲሆን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳስበዋል ሲል የአዲስ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
የኮሙንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ሚያዚያ 22/2017

10ኛው የኦዲተሮች ልምድ ልውውጥ በድሬደዋ

10ኛው ሀገር አቀፍ የዋና ኦዲተሮች ውይይት በድሬደዋ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 10ኛው የክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶች የምክክር እና የልምድ ልውውጥ መድረክ በድሬደዋ ከተማ እየተካሄደ ነው።የድሬደዋ አስተዳደር ዋና ኦዲተር ፋኪያ መሐመድ በዚህ ወቅት÷የጋራ ምክክሩ ደረጃውን የጠበቀ የኦዲት ተግባራት በማከናወን የመንግስትና የህዝብ በጀት በአግባቡ ለታለመለት ተግባር እንዲውል የሚያስችሉ ግንዛቤዎችን ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል።
የልምድ ልውውጡ ደረጃውን የጠበቀ የክዋኔ ኦዲት ለመተግበር የሚያስችል ግንዛቤ የሚፈጥር መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡በተጨማሪም በየደረጃው በሚገኙ ተቋማት ውስጥ የተጠያቂነት ሥርዓትን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል መደላድል እንደሚፈጥር ነው የገለፁት፡፡በውይይቱ ላይ የድሬደዋ አስተዳደር ምክርቤት አፈጉባዔ ፈትሂያ አደን፣ የየክልሎች እና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ዋና ኦዲተሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ለሶስት ቀናት በሚዘልቀው ውይይት ላይ ለተሞክሮ የሚያግዙ የተለያዩ ሰነዶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው የገኛል።

ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል

 “ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል” ቢሚል ርዕስ ከባለ ድርሻ አካላት (ኦዲት ተደራጊ ተቋማት) አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ።

መጋቢት 23/2017 ዓ.ም

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከባለድርሻ አካላት (ኦዲት ተደራጊ ተቋማት) አመራሮች ጋር “ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል”  በሚል ርዕስ ላይ በጁፒተር ሆቴል ውይይት አደረገ። ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ የውይይቱን ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን፤ በቀረበውም ሰነድ ላይ ተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየት ሰጥተዋል።

በመጨረሻም በቀረበው ጥያቄ ላይ  የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ የተከበሩ አቶ ማሾ ኦላና እና ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ  ምላሽ ሰጥተውበት ውይይቱ ተጠናቅቋል።

የ2016 ዓ.ም እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ አደረገ።

 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት የመ/ቤቱ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት በዛሬው ቀን ማለትም በ20/12/2016 ዓ.ም በኢትጵያ ስራ አመራር ኢንስቲትውት በዕቅድና በጀት ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ማሞ አማካኝነት ቀርቧል።

በመጨረሻም  በቀረበው ሰነድ ላይ የመ/ቤቱ ሰራተኞች አስተያየት እና ጥያቄ ያነሱ ሲሆን ለተነሱት ጥያቄዎች እና  አስተያየቶች የመ/ቤቱ ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ መልስ ሰጥተውበት ግምገማው ተጠናቅቋል።