የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በልዩ ኦዲት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አጠናቀቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በልዩ ኦዲት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አጠናቀቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለአምስት ተከታታይ ቀናት በልዩ ኦዲት ላይ ያጠነጠነ ስልጠና ለልዩ ኦዲት ባለሙያዎቹ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ እንዳሉ በልዩ ኦዲት ስራዎቻችን የተቀመጡትን አለማቀፍ ስታንደርዶች በመጠበቅ ባለበጀት መ/ቤቶች የተበጀተላቸውን የህዝብ ሃብት በአግባቡ መጠቀማቸውን ለማረጋገጥና በማወቅም ሆነ በለማወቅ ለሚሰሯቸው ስህተቶች መፍትሄ እዲያበጁ ማስቻል እንዲሁም የሀገርና የህዝብን ሀብት ከብክነት ለመጠበቅና አንደ አንድ የመንግስት ኦዲት አድራጊ ተቋም ሁሉም የኦዲት ባለሙያ ሚናውን እንዲወጣ ለማስቻል ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡
ዋና ኦዲተ አመንቴ መቻሉ አክለው የኦዲት ግኝትና ሂሳብ ጉለት ሲገኝ ገንዘብ ተመላሽ ማድረግ ብቻ ሳይሆን የተጠያቂነት አሰራር ስርዓትን ለማስፈን አስፈላጊውን የህግ ሂደት በመከተል ግልፀኝነትና የተጠያቂነት አሰራር ስረዓት እንዲሰፍን መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በስልጠናው ማብቂያ በሰጡት አስተያየት ስልጠናው በቀጣይ ስራቸው ላይ የተሻለ አቅም የሚሰጡ ጠቃሚ እውቀትና ክህሎቶችን ያስጨበጣቸው መሆኑን ጠቅሰው በተለይ በልዩ ኦዲት ስራ ላይ ሊሚያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችና ስጋቶችን በግልፅ ያመላከተ በመሆኑ የልዩ ኦዲት ስራዎቻችንን ውጤታማ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል፡፡
የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም




Leave a Reply