“ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት”
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን የመስሪያ ቤቱ አመራርና ሰራተኞች በተለያዩ ሁነቶች አከበሩ፡፡
********************************
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አምንቴ መቻሉ በመርሀ-ግብ ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሚያዝያ 21 ቀን 1998 ዓ.ም ባካሔደው ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባው ላይ የኤፌዴሪ ህገ መንግስት የፀደቀበትን ህዳር 29 ቀን የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ተብሎ በአገር አቀፍ ደረጃ እንዲከበር ሲወስን የውሳኔው ዓላማ የኢትዮጵያ ህዝቦች መክረውና ፈቅደው ያጸደቁት ህገ-መንግስት ያስገኘላቸውን ጥቅሞች እንዲያስቧቸው መብቶችና ነጻነቶቻቸውን ጠብቀው ማቆየት ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ የሚተዋወቁበት ባህላቸውን፣ ቋንቋቸውንና ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት፤አገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚወያዩበት፤ የጋራ እምነቶቻቸውንና ተስፋቸውን የሚጋሩበትን ሁኔታ ለመፍጠር ነው ብለዋል፡፡
ዋና ኦዲተር አምንቴ መቻሉ አክለው የብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በ1999 ዓ.ም በፌዴሬሽን ምክር ቤት አዘጋጅነት ”ሕገ-መንግስታዊ ቃል ኪዳን የአብሮነታችን መገለጫ ነው” በሚል መሪቃል በአዲስ አበባ ከተማ የተከበረ ሲሆን ይህም ላለፉት 19 ዓመታት በተከታታይ በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር መቆየቱን ገልፀው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለሕብረ ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል ሂዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሚከበር መሆኑን ጠቅሰው የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤትም ከዚህ በመነሳት ይህን ህገ-መንግስታዊ ዋስትና የተረጋገጠበት የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ ይገኛል ብለዋል፡፡
ለተሳታፊዎች የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት የኮልፌ ክ/ከተማ የብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ት/ቤት የማስፈፀም የአቅም ግንባታ ስራዎች አስተባሪ አቶ ፍቃዱ ቀቀባ አስተባባሪ እንዳሉት የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብት መከበር ሕገ መንግሥታዊ ዋስትና ያረጋገጠው የኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት የጸደቀበትን ቀን ህዳር 29 በየዓመቱ በተለያዩ ሁነቶች ላለፉት 19 ዓመታት ሲከበር መቆየቱን አስታውሰው በዚህ አመት “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል ለ20ኛ ግዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ሲከበር በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ፌዴራላዊ ሥርዐት ማእቀፍ የተገነባ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ሥር እንዲሰድና እንዲዳብር ማደረግን አላማ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡
********************************
ህዳር 19/2018 ዓ.ም
የኮምንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት



































