Archives June 2026

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና የተጠሪ ተቋማትን የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ገመገመ።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና የተጠሪ ተቋማትን የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ገመገመ።
ጥር 04/04/2018 አዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ፣ ለምክር ቤቱ ተጠሪ ከሆኑ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።
በመድረኩ ላይ ሁሉም ተጠሪ ተቋማት የስድስት ወር እቅድ አፈጻጸማቸውን ያቀረቡ ሲሆን በተለይም እንደ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ሪፎርም ያደረጉ ተቋማት ሪፎርሙ ያመጣው ለውጥና ተግዳሮቶችን ላይ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመልካም አስተዳደር ፤ሙስናን ከመከላከል አኳያ እና ከሌብነትና ከብልሹ አሠራር አንፃር በከተማዋ ለታየው የልማት ስራ ስኬት ተቋማቱ ስላበረከቱት ድርሻ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የውይይት መድረኩን የመሩት የምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ የተከበሩ ዶ/ር ማሾ ኦላና፤ ተጠሪ ተቋማቱ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ የታቀዱ ስራዎችን ብቻ ሳይሆን፣ ከዚያም በላይ የሆኑ ተግባራትን በፍጥነትና በጥራት ማከናወናቸው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም ተቋማቱ እርስ በእርስና ከሌሎች አካላት ጋር በቅንጅት በመስራታቸው ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡን ተናግረዋል፤ በተጨማሪም የላቀ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማረጋገጥ ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ጭምር ገልፀዋል።
የመንግስት ዋና ተጠረው፤ በተጨማሪም የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ማጠናከር፣ የህጎችን ተፈጻሚነት በኦዲት መፈተሽ እና የህዝብና የመንግስት ሀብት በግልጽነትና በተጠያቂነት መመራቱን ማረጋገጥ እንደሚገባ አቅጣጫ አሰቀምጠዋል።
የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ማሾ ኦላና አክለውም፣ በባለፈው በጀት ዓመት የታዩ መልካም አፈጻጸሞችን በማስቀጠልና ውስንነቶችን በመለየት ተቋማዊ ጥንካሬን መገንባት እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ የተሳተፉ የተጠሪ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች በበኩላቸው፣ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ቀሪ የትኩረት ስራዎችን እንደሚያከናውኑ ገልጸዋል። የከተማውን ነዋሪ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በህግ የተሰጣቸውን ስልጣንና ኃላፊነት በመጠቀም በትጋት ለመስራት ቃል ገብተዋል.። የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ክዋኔ ኦዲት ዋና አላማ ለመልካም አስተዳደር፣ ለተጠያቂነት እና ለግልፀኝነት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግን ያለመ ነው።

ክዋኔ ኦዲት ዋና አላማ ለመልካም አስተዳደር፣ ለተጠያቂነት እና ለግልፀኝነት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግን ያለመ ነው።
***********************************************
በአሁኑ ወቅት የተቋማትን ስራ ውጤታማነት ለማረጋገጥና አላስፈላጊ ብክነትን ለመቀነስ የክዋኔ ኦዲት (Performance Audit) ወሳኝ መሆኑ የታመነ ነው። የክዋኔ ኦዲት ተቋማት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በምን ያህል ደረጃ እየተወጡ እንደሆነ የሚመዘንበት አይነተኛ መሳሪያ በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩን ተቋማት አፈፃፀም የተሻለ ለማድርግ በሶስት ዙር ለተመረጡ ከከተማ አስተዳደሩ ለተውጣጡ የውስጥ ኦዲተሮች የክዋኔ ኦዲት ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡

ለሁለተኛ ዙር የክዋኔ ኦዲት ስልጠና የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲት መስሪያ ቤት የክዋኔ ኦዲት ማናጀር የሆኑት አቶ መስፍን ውቤ እንዳሉት የአፈጻጸም/ክዋኔ ኦዲት አንድ ተቋም ግቡን ለማሳካት ሀብቱን እንዴት በብቃት እንደሚጠቀም የሚመረምር ገለልተኛ፣ ተጨባጭ እና አስተማማኝ ግምገማ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ ቅልጥፍናና ውጤታማነትን በመገምገም፣ መሻሻል ያለባቸውን ቦታዎች በመለየት ለተቋማት የላቀ አፈፃፀም ምክረ ሃሳብ በማቅረብ በትኩረት የሚሰራ ነው ብለዋል።

አቶ መስፍን አክለው የክዋኔ ኦዲት በዋናነት በሶስት የ”E” መርሆዎች፤ Economy/ቁጠባ Efficiency/ብቃት Effectiveness/ውጤታማነትን አጣምሮ የያዘ መሆኑን ጠቅሰው የክዋኔ ኦዲት በመንግስት ሴክተር ተቋማት ውስጥ ለተሻሻለ ኢኮኖሚ፣ ቅልጥፍና እና ውጤታማነት አስተዋፅኦ በማድረግ፤ ለመልካም አስተዳደር፣ ለተጠያቂነት እና ለግልጽኝነት አሰራር የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግን ዓላማ ያደረገ የኦዲት ዘርፍ ነው ብለዋል፡፡
*****************************************
መጋቢት 3/2018 ዓ.ም

ኦዲተሮች የሚባክነውን ውስን የመንግስት እና የህዝብ ሀብት ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ፡፡

ኦዲተሮች የሚባክነውን ውስን የመንግስት እና የህዝብ ሀብት ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ፡፡

በተለያዩ ተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉ የማጭበርበር Fraud ድርጊቶችን ተከትሎ የልዩ ኦዲት አስፈላጊነት እና ሚና በከፍተኛ ሁኔታ ትኩረት እየሳበ ይገኛል መንግስታዊና የግል ተቋማት ሙስስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከልና ተጠያቂነትን ለማስፈን ተቋማት መፍትሄ የሚሏቸውን አማራጮች ሲወስዱ ይስተዋላል ይሁን እንጂ በሚፈለገው ልክ ውጤት አምጥቷል ለማለት አያስደፍርም።

በመሆኑም የማጭበርበር ተግባራት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት ለማስቀረት በእውቀትና በክህሎት የሚመራ ኦዲተር ማፍራት ወሳኝ ሚና ያለው በመሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከከተማ አስተዳደሩ ለተውጣጡ የተመረጡ የውስጥ ኦዲተሮች ስለ ማጭበርበር/ ፍራውድ ተግባራት በሶስት ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

የአዲ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ ለሰልጣኞች ባስተላለፉት መልዕ እንዳሉት ተቋማት በአሰራራቸው ቀልጣፋና ፍትሀዊ አገልግሎት ከመስጠት ይልቅ በሙስናና ብልሹ አሰራር ምክንያት ተገልጋዩንና ህብረተሰቡን በአግባቡ ማገልገል ካልቻሉ ህብረተሰቡ በተቋሙ ብሎም በመንግስት አመኔታ ሊያጣ ይችላል ይህ እንዳይሆን ግን የሚሰሩ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ቀድሞ የመቆጣጠርና ተፈፅሞ ሲገኝም ተገቢ ማስተከካከያ እንዲሰጥ ለማድረግ የኦዲተሩ ሚና የላቀ ነው ብለዋል።

ዋና ኦዲተሩ አክለው ሙስናና ብልሹ አሰራር የሀገር ኢኮኖሚን በእጅጉ የሚጎዳ መሆኑን ጠቅሰው በተቋማት ውስጥ ያሉ ሁሉም የውስጥ ኦዲተሮች በያገባኛል ስሜት የሚባክነውን ውስን የመንግስት እና የህዝብ ሀብትን ከብክነትና ብልሹ አሰራር ለመታደግ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ለሠራተኞች የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ

በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ለሠራተኞች የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ
***********************************
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ እንደገለፁት መልካም ስነ ምግባርና ሙስናን መዋጋት ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ሳይሆን የእያንዳንዱ ሰራተኛ ድርሻና ተሳትፎ መሆኑን በመጥቀስ ሰራተኛው ስራውን በቅንነትና በታማኝነት በመስራት ለሌሎች አርአያ መሆን ይገባል ብለዋል፡፡

አክለውም የዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የከተማዋን ሀብትና ንብረት በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚያረጋግጥ ተቋም እንደመሆኑ መጠን የማጭበርበር ወይም የልዩ ኦዲትን በዳይሬክቶሬት ደረጃ በአዲስ መልክ በማደራጀት ሙስናንና ማጭበርበርን በመፋለም በግምባር ቀደምትነት የሚጠቀስ እንደመሆኑ ፣ የሠራተኞቹ የሥነ-ምግባር ደረጃ ከማንኛውም ተቋም በላይ አርአያነት ያለው ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።

የመንግስት ልማት ድርጅት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳሬክቶሬት አቶ ንጉስ ሽመልስ በበኩላቸው ሙስናን መከላከል የሚቻለው በጠንካራ የሕግ ተፈጻሚነት ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱ ሠራተኛ የሥነ-ምግባር ባለቤት ሲሆንና የሙስናን አፀያፊነት በልኩ ሲረዳ መሆኑን ጠቅሰው ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በሥራ ላይ የሚያጋጥሙ የሥነ-ምግባር ብዥታዎችን ለመቅረፍና ሙያዊ ግዴታን በብቃት ለመወጣት የተሻለ ግንዛቤ መፍጠርን ያለመ ነው ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በቀጣይም የሙስና መከላከል ስትራቴጂውን በማጠናከር፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሠራር ለመገንባት እንደሚሠራ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ ገልፀዋል።
*********************************
ሚያዝያ 9/2018 ዓ.ም
የኮሙንኬሽን ዳይሬክቶሬት

4ኛው የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተሮች አመታዊ የምክክር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል፤

4ኛው የፌዴራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተሮች አመታዊ የምክክር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል፤
በጉባኤው የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉን ጨምሮ ሌሎች የክልል እና የከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተሮች ተሳትፈውበታል፡፡
በጉባኤው ላይ የተገኙት የዘርፉ አመራሮች በዋናነት በፌዴራል በክልሎች እና በከተማ አስተዳደሮች መካከል ያለውን የኦዲት አሰራር ለማዘመን እና የተሻሉ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ የሚያስችል መድረክ መሆኑ ታምኖበታል፡